1፤ የእግዚአብሔር ሰው ሙሴ ሳይሞት የእስራኤልን ልጆች የባረከባት በረከት ይህች ናት።
2፤ እንዲህም አለ።
እግዚአብሔር ከሲና መጣ፥
በሴይርም ተገለጠ፤
ከፋራን ተራራ አበራላቸው፥
ከአእላፋትም ቅዱሳኑ መጣ፤
በስተ ቀኙም የእሳት ሕግ ነበረላቸው።
3፤ ሕዝቡንም ወደዳቸው፤
ቅዱሳኑ ሁሉ በእጅህ ናቸው፤
በእግሮችህም አጠገብ ተቀመጡ፤
ቃሎችህን ይቀበላሉ።
4፤ ሙሴ ለያዕቆብ ጉባኤ ርስት የሆነውን
ሕግ አዘዘን።
5፤ የሕዝቡ አለቆች ከእስራኤል ነገዶች
ሁሉ ጋር በተከማቹ ጊዜ፥
ንጉሥ በይሹሩን ነበረ።
6፤ ሮቤል በህይወት ይኑር፥ አይሙት፤
ሰዎቹም በቍጥር ብዙ ይሁኑ።
7፤ የይሁዳ በረከት ይህ ነው፤ እንዲህም አለ።
አቤቱ፥ የይሁዳን ድምፅ ስማ፥
ወደ ወገኖቹም አግባው፤
እጆቹ ይጠንክሩለት፤
በጠላቶቹ ላይ ረዳት ትሆነዋለህ።
8፤ ስለ ሌዊም እንዲህ አለ፥
ቱሚምህና ኡሪምህ ለቅዱስህ ሰው ነው፥
በማሳህ ለፈተንኸው፥
በመሪባ ውኃም ለተከራከርኸው፤
9፤ ስለ አባቱና ስለ እናቱ። አላየሁም ላለ፥
ወንድሞቹንም ላላስተዋለ፥
ልጆቹንም ላላወቀ፤
ቃልህን አደረጉ፥
ቃል ኪዳንህንም ጠበቁ።
10፤ ፍርድህን ለያዕቆብ፥
ሕግህንም ለእስራኤል ያስተምራሉ፤
በፊትህ ዕጣንን፥
በመሠዊያህም የሚቃጠል መሥዋዕት ይሠዋሉ።
11፤ አቤቱ፥ ሀብቱን ባርክ፥
የእጁንም ሥራ ተቀበል፤
የሚነሣበትን ወገብ ውጋው፥
የሚጠሉትም አይነሡ።
12፤ ስለ ብንያምም እንዲህ አለ።
በእግዚአብሔር የተወደደ በእርሱ
ዘንድ ተማምኖ ይኖራል፤
ቀኑን ሁሉ ይጋርደዋል፥
በትከሻውም መካከል ያድራል።
13፤ ስለ ዮሴፍም እንዲህ አለ፥
ምድሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተባረከ ይሁን፤
በሰማያት ገናንነት በጠል፥
በታችኛውም ቀላይ፥
14፤ በፀሐዩ ፍሬያት ገናንነት፥
በጨረቃውም መውጣት ገናንነት
Friday, February 12, 2010
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment